የቀድሞ የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ ጎሳዬ ጎዳና እና አዲስ የተመደቡ ሀላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበረ ጋር ትውውቅና የስራ ርክክብ አደረጉ
አዲሱ የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ አቶ አሻግሬ ጀምበረ ቢሮ በሀላፊነት ሲመሩ ከቆዩት ከአቶ ጎሳዬ ጎዳና ጋር ትውውቅና የስራ ርክክብ አድርገዋል።
አዲሱ የቢሮ ኃላፊ ከቢሮዉ ምክትሎችና ከሌሎች ሥራ ኃላፊዎች ጋር ትዉዉቅ በማድረግ በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ዉይይት አድርገዋል።
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባለፉት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን ግምገማ ተከትሎ አዲስ የስልጣን ምደባና ሽግሽግ ማድረጉ የሚታወስ ነዉ።
ሀዋሳ፣ መስከረም 26/2018 ዓ.ም የሲዳማ ክልል ኢ/ልማት ቢሮ የህ/ግን/ዳይረክቶሬት